Keith Sain

Creative Manager

In hac habitasse platea dictumst. Curabitur eget dui id metus pulvinar suscipit. Quisque vitae ligula laoreet, scelerisque leo quis, facilisis metus. Sed pellentesque, urna sed varius consectetur, eros augue fringilla magna, id elementum sem magna vel diam. Nulla sed hendrerit nunc.
In hac habitasse platea dictumst. Curabitur eget dui id metus pulvinar suscipit. Quisque vitae ligula laoreet, scelerisque leo quis, facilisis metus. Sed pellentesque, urna sed varius consectetur, eros augue fringilla magna, id elementum sem magna vel diam. Nulla sed hendrerit nunc.

ጎጊባ አነ/የፋይ/ተቋም አ.ማ

About

About us

ጎጊባ አነ/የፋይ/ተቋም አ.ማ
Gogiba Microfinance Institution S.C
1.መግቢያ
ጎጊባ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እ.እ.አ በመጋቢት 15/2022 ባገኘዉ የሥራ ፈቃድ መሠረት በደቡብ ምዕራብ ክልል ፈር ቀዳጅ የሆነ የፋይናንስ ተቋም በመሆን ዋና መ/ቤቱን በክልሉ በማድረግ የማይክሮ ፋይናንስ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ክልል ሀብት የሆነ ብቸኛ የፋይናንስ ተቋም ነዉ"
ተቋሙ በክልሉ ባሉት ዞኖችና ወረዳዎች 6 ቅርንጫፎች 3 ሳታላይቶች እንዲሁም 3 የአገልግሎት ማዕከላት በመክፈት ሁሉንም መዳረሻዎች በኮር ባንኪንግ ስስተም በማስተሳሰር አገልግሎት እየሰጠ ያለ ተቋም ነዉ።
ጎጊባ የአካባቢያችንን ሀብት ለአካባቢ ስራ ዕድል የሚል አስተሳሰብ አንግቦ ወደ ስራ የገባ ሲሆን እስከ ህዳር 30/2024 ድረስ ከ15,401 በላይ የቁጠባ እና ከ965 የሚልቁ የብድር ደንበኞች ያሉት ሲሆን በብድር ስርጭትም ከ 68ሚልዮን ብር በላይ ከአካባቢዉ ማህበረሰብ በመሰብብ በክልላችን ወደ ስራ ለመግባት ለሚፈልጉ የህብረተሰብ ክፍሎች ብድር በማሰራጨት ለአላማቸዉ ስኬት የድርሻዉን በመወጣት ላይ ይገኛል ።
 

2.የተቋሙ ራዕይ (Vision)
ከደቡብ ምዕራብ ክልል ፈልቆ መላ ኢትዮጵያን እያዳረሰና እያስተሳሰረ የሚሽከረከር የማይነጥፍ የሞላ የገንዘብ አፍላግ የድህነትን ምሽግ እየደረማመሰ ብልፅግናን የሚያጎናፅፍ ተመራጭ ግዙፍ ሥኬታማ የላቀ ባንክ ሆኖ ማየት "
 

3. እሴቶች (Values)
    የደንበኞች እርካታ የተቋሙ የህልዉና መሠረት ነዉ፡፡
    ሁሌም ለለዉጥና ለአገልግሎት ዝግጁ ነን፤
    ከራስ ይልቅ ለደንበኞቻችን ተጠቃሚነት ቅድሚያ እንሰጣለን
    የሰዉ ሀብታችን ትልቁ የተቋማችን የህልዉና መሰረት ነዉ፤ 
    ቁጠባ መር የብድር አገልግሎት ባህል እንዲጎለብት እንተጋለን።
 

 

 4.ግብ (Mission)
    በአጭር ጊዜ ወደ ባንክ ማደግ ነዉ።
 

 

 

5. ዓላማዎች (Objectives)
    ለሴቶችና በኢኮኖሚ አቅም ለሌላቸዉ ቅድምያ በመስጠት የፋይናንስ አማራጮችን በመዘርጋት የምግብ ዋስትና እንዲረጋገጥ ማድረግ
    በስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ቋሚ፣ ዘላቂና ትርፋማ ስራዎችን በመስራት ልማትን ማፋጠን 
    የተቀላጠፈ የፋይናንስ አገልግሎት ለደንበኞቻችን በመስጠት በኢኮኖሚ ዕድገት ላይ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን መደገፍና በኢኮኖሚ ንቁ ማህበረሰብ መፍጠር
 

 

Learn more